Tuesday, May 27, 2014

“ኀሊናዬን ከጕድፍ ለማዳን ስለምፈልግ [የመዝሙር] ክሊፕ አላይም”




ማስታወሻ፦ ይህን ቃለ ምልልስ ያደረግሁት በየሣምንቱ እየታተመ ከሚወጣውናፋክትከተሰኘው መጽሔት ጋር ነው። 307 ሰዓት ከወሰደው ቃለ ምልልስ ውስጥ በጋዜጠኛው ተመርጠው በግንቦት 9 ቀን 2006 . በመጽሔቱ ቍጥር 46 ላይ የታተሙትን ጥያቄዎችና የኔን ምላሽ ያላገኛችሁት ታነብቡት ዘንድ ከመጽሔቱ ላይ በመቅዳት እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ። 

ለዚህ ቃለ ምልልስ በርእስነት የቀረበው ሐሳብ በእኔ ንግግር ውስጥ ያለ ቢኾንም በርእስነት ያኖርሁት ግን  እኔ አይደለሁም። 

ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን። መልካም ንባብ። 

  • ስለ እግዚአብሔር የማይጠየቅ (ሊጠየቅ የማይገባ) ጥያቄ ይኖራል?


እንደ ኹኔታው ነው።እግዚአብሔር ማን ነው?” ከሚለው የገዘፈ ጥያቄ ያለ አይመስለኝም።እርሱ ማን ነው?” ተብሎ መጠየቅ እስከ ተቻለ ድረስ ደግሞ፣ እግዚአብሔርን የሚመለከት ጥያቄ በቅንነት ማንሣት ይቻላል ብዬ አስባለሁ።
  •  ማንሣትማ ይቻላል።የማይቻል አለ ወይ?” ነው ጥያቄው።


የለም። የክብሩን ዕውቀት ብርሃን ለመስጠት በሰው ልብ ውስጥ ሲበራ እፎይ የሚያሰኝ አምላክ እንደ መሆኑ፣ የትኛውንም ጥያቄ ማንሣት ይቻላል።

  •  ለምን መሰለዎት ይህን ጥያቄ የማነሣልዎ? አንዳንዶች በአምላክ ዙሪያ ጥያቄህ ሲበዛ እምነትህ ጥርጣሬ ውስጥ የገባ ይመስላቸዋል። ግን ደግሞ ያንኑ ጥያቄ  እነዚሁ አንዳንዶች የማያነሡት ስለገባቸው ሳይኾን ማንሣት አይገባም ብለው ስለሚያምኑ ነው። ጥያቄው “‘እግዚአብሔር ይህን አትጠይቁኝያለው ሐሳብ አለ ወይ?” ነው።


በአንድ በኩል የለም። በሌላ በኩል አለ። በጠያቂው ማንነትና የመነሻ ፍላጎት ላይ የሚወሰኑ ጥያቄዎች ይኖራሉና። አንዳንዱ ጠያቂ በተፈታታኝነት መንፈስ ተገፋፍቶ ሊጠይቅ ይችላል። እግዚአብሔርን ለማወቅ ከሚደረግ የእምነት ፍለጋ ሳይኾን፣ ከተዐብዮ መዳፈርናየአምላክን አለመኖር ላረጋግጥከሚል ከንቱ ስንፍና ወይም ከክሕደት የሚመነጭ የመፈታተን ጥያቄ ጠያቂዎች አሉ። የእግዚአብሔርን ተላቅነትና በሥራው ሁሉ ሊነገር የማይቻለውን ጥበቡን ከመካድ እንዲሁም ዐመፃ ከተሞላ ልቡና የሚቀዳ የዘባችነት ጥያቄ ይኖራል። አየህ፤ ኀጢአት ሰዎች በአግባቡ እንዳያስቡና የእግዚአብሔርን ሀልዎት እንዲክዱ ሊያደርጋቸው ይችላል።

ሌሎች ደግሞ አምላክ ሊኖር ይችላል ከሚል የመነሻ ሐሳብ ይጀምሩናግን እሱ ማን ነው? ላውቀው እችላለሁ ወይ? ራሱን የሚገልጥስ ነው ወይ?” በማለት በቀና መንፈስ የሚጠይቁ ይኖራሉ። በሦስተኛ ደረጃ የሚገኙ ጠያቂዎች ደግሞ ምእመናን ናቸው። አማኞች ሆነው ሳለ እምነታቸው በተፈተነና ዙሪያ-ገባው በተናጋ ጊዜ ወይም ደግሞ ከሚደርስባቸውና በዙሪያቸው ከሚያዩት ነገር ተነሥተው የሚያነሡት ጥያቄ ይኖራል።

ታዋቂና ስሞቻቸው በቅዱሳት መጻሕፍት የተጠቀሱ ቅዱሳን ጭምር በዚህ ደረጃ ጥያቄ አንሥተዋል።የእነዚህ ጥያቄ በህላዌው ላይ ያነጣጠረ አይደለም። ነገር ግን በዙሪያቸው የከበባቸው ነገር ከእግዚአብሔር ባሕርይና ሥራ ጋር አልገጣጠም ያለ ሲመስላቸው የሚያነሡት ጥያቄ ይኖራል። በአጠቃላይ ጥያቄው በማንና በምን መንገድ ተነሣ የሚለው የሚወስነው ይመስለኛል።

  •   የምናያቸው ብዙ ነገሮች ፍትሐዊ አይደሉም። ጕድለት አላቸው።እግዚአብሔር በርግጥ አለ? ካለ እንዴት ይህ ሲሆን ዝም አለ?” የምንልባቸው ብዙ ጥያቄዎች በውስጣችን አሉ። በአንዳንድ ሁኔታዎች የተነሣ የእግዚአብሔርን መኖር በራሱ ጥያቄ ውስጥ ማስገባት ያልተገባ ይሆናል? ለምንድነው ማመን ብቻ ያለብን?


ማመን ያለብንማ ያለ እምነት እግዚአብሔር ደስ ማሰኘት ስለማይቻል ነው። ደግሞም ያለ እምነት አናገኘውም። በዚህ ኀጢአተኛ ዓለም እግዚአብሔር ወደ እምነት ሊያመጣን እንደሚገባ መታወቅ አለበት። በርግጥ አንተ ባልኸው መንገድ ጥያቄ የሚሠነዝሩ ቅን ጠያቂዎች ሊኖሩ ይችላሉ። የእስራኤል መስፍን የነበረው ጌዴዎን ጠይቋል። ሐዋርያው ቶማስንም ውሰደው። የክርስቶስ ትንሣኤን ብሥራት ከሌሎቹ ቢሰማምካላየሁ አላምንምብሎ ነበር። ይህን ጥያቄ በማንሣቱ እንደ መናፍቅ አልተፈረጀም። ማረጋገጫ የፈለገ ጠያቂ ነበር። እነዚህ ጠያቄዎች ግን መነሻቸው እምነት እንጂ የጥያቄያቸው መሠረት የእርሱን ህላዌ የመጠራጠር አይደለም።

ዛሬም ጥያቄ ማንሣቱ ላይ አይደለም ችግሩ ያለው። የእኛ ጥያቄዎች የሚነሡት ከቆምንበት አድማስና የእይታ መስመር ተቀንብበው እመሆኑ ላይ ነው። ነገሮችን ከዘላለም አንጻር አናያቸውም። የጊዜውን ብቻ ነው የምንመለከተው። ከመላለሙ (ዩኒቨርስ) በላይ ከፍ ያለው ልዑል አምላክ፣ የዓለሙን ሁኔታ፣ የሰው ልጆችን ሕይወት፣ ጠቅላላውን የአጽናፈ ዓለም ንድፍ ከዘላለማዊ ሐሳቡና ከጠለቀ ዕውቀቱ ስፋት ይመለከተዋል። እያንዳንዱን ጥቃቅን  ነገር እኛ ውሱንና ኀጢአተኛ የኾንነው ፍጡራን እግዚአብሔር ከሚያይበት ኹኔታ ማየት የማንችልበት ውሱንነት ጥያቄያችን እንዲገዝፍ ሊያደርገው ይችላል። ከዘላለም አንጻር እኛ በጊዜ የተገደብን ነን፤ ሁሉን እንደ ፈቃዱ ምክር ከሚሠራው ታላቅ አምላክ አንጻር ደግሞ እኛ ኢምንት ፍጡራን ነን። ስለዚህ በተነሣው ርእሰ ጕዳይ አኳያ አተያያችንና ብያኔያችን ስሑት የመኾን ዕድሉ ሰፊ ነው። መረሳት የሌለበት ዋነኛ ነገር ደግሞ ኀጢአትና መዘዙ ያወሳሰበው ብዙ ነገር መኖሩን ነው።

  • መንፈሳዊ ሰው ስንኾን የዚህ ዓለም ህማምና ሥቃዮች ይቀሩልናል? ወይስ እነርሱ እንዳሉ የምንቋቋምበት ኀይል እናገኛለን?


አይቀርልንም። አማኞች ከዓለም ባንኾንም (ዓለማዊ ባንኾንም) እንኳ፣ በዓለም ውስጥ የምንኖር ግን ነን። ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔርን ክብር የምታንጸባርቅና እውነተኛውን መንፈሳዊ ሕይወት በተባረከው ኅብረቷ ጭምር የምታሳይና በውጭ ላለው የተሰበረ ዓለም የምታበራ የወንጌል ባለአደራ ናት። ይሁን እንጂ ያለችው በዚሁ መከራ ባልተለየው ዓለም ውስጥ ነው። መንፈሳዊነት አጠቃላይ የንጽረተ ዓለም ለውጥ ነው የሚሰጥህ። ክርስቲያን መሆኔ በዚህ ዓለም መከራ እንዳይደርስብኝ የሚከላከል ዋስትና አልሰጠኝም። መጽሐፍ ቅዱስ ቃል በቃል፣በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁነው የሚለን። እንዲያውም እምነታችንን ተከትሎት የሚመጣ መከራ ሊጨምርብን ሁሉ ይችላል።በክርስቶስ ለማመን ብቻ ሳይሆን ስለ ስሙ መከራ እንድትቀበሉ ነው የተጠራችሁትይልሃል። ነገር ግን መከራን የምንረዳበት የእይታ ለውጥ እናገኛለን። መንፈሳዊ ስትሆን ከምትችለው በላይ ፈተና እንደማይመጣብህ ትረዳለህ። እግዚአብሔር ከፈተናህ መውጫውን እንደሚያዘጋጅልህም ታውቃለህ። ደግሞም መከራው በእምነትህ  እንድትጠነክር፣ በሕይወትህ እንድትበረታና በትዕግሥት እንድትጸና መሣሪያ ሊሆን መቻሉን ወዘተታምናለህ። ክርስትናን ከመከራ የማምለጫ አቋራጭ መንገድ አስመስለው የሚያስተምሩ ዘመነኛ መምህራን አስተምህሯቸው ዐንካሳ ስለሆነ ጥያቄ ላይ ወድቋል። ክርስትና መንገዱ የመስቀል እኮ ነው!
  •   እግዚአብሔርን በምንድነው ያወቅነው?


ጥሩ ጥያቄ ነው። እግዚአብሔርን ያወቅነው በአስተርእዮው [በመገለጡ] ነው። እግዚአብሔርን ልናውቀው የምንችለው ራሱን ስለ ገለጠ ነው፤ ራሱን ባልገለጠበት ሁኔታ ማንም ሊያውቀው አይችልምና። ዓለም በገዛ ጥበቧ እግዚአብሔርን ማወቅ ስላልቻለች የመንፈስን ኀይል በመግለጥ ማለትም በእግዚአብሔር ኀይል እንጂ በሰው ጥበብ ላይ እንዳይመሠረት ሆኖ ነው የተገለጠው።
  •  ምን ማለት ነውራሱን መግለጥ? በእንደምን ያለ ኹኔታስ?

አስተርእዮው በአጠቃላይም በልዩ መንገድም ነው። እግዚአብሔር ራሱን የገለጠበት/የሚገልጥበት መንገዶች አሉት። አንደኛው ዐይነት አጠቃላይ ነው። ለሁሉም ሰዎች፣ በየትኛውም ስፍራና ሁልጊዜ ያለ ነው። በአንድ የተወሰነ ወቅትና ለተወሰኑ ሰዎች ወይም ለአንድ ሰው ብቻ የሚሰጥ አይደለም። ምን ማለቴ ነው? እግዚአብሔር መላለሙን ፈጥሮ የተወ አምላክ አይደለም። መላለሙን የፈጠረ እንደ መኾኑ በቀጣይነት በመግቦቱ አጽንቶ ይዞታል።

ይህ የተሠራው ዓለም ዝም ብሎ፣ በዘፈቀደና እንዳጋጣሚ የተገኘ ያለመኾኑን ይልቁኑም አስገኚ አምላክ እንዳለው ፍጥረት ውስጣዊ ግንዛቤ ይሰጠናል። ስለዚህ ሰው እንደ መሆናችንየዚህ ዓለም ፈጣሪ አምላክ አለብለን ልናምን እንችላለን። (በፈለከው ስም ብትጠራውም እንኳ) ከፍጥረት ተነሥተህ እንዲሁም በሰው ኅሊና ምክንያት ስለ እግዚአብሔር ሀልዎት የሚኖርህ ውስጣዊ ግንዛቤ ሰው ከመኾን ጋር የተቈራኘ ነው። ሕፃናት እንኳ ሳይቀር ይህን መሳይ ዝንባሌ እንዳላቸው አንዳንድ የሥነ ሰብ ተመራማሪዎች ጭምር ይናገራሉ። ከፍ ሲሉ በተለያየ ሐሳብ ተደብድቦ ከውስጣቸው በመምከኑ ምክንያት አላማኝ ካልሆኑ በቀር ውስጣቸው የመንፈሳዊነት ዝንባሌ አለ።

  • አጠቃላዩ መገለጥ ሰዎች እውነተኛውን አምላክ በትክክል እንዲረዱት (እንዲያውቁት) ሊያደርጋቸው ይችላል?

ልመጣልህ ነው። አጠቃላዩ መገለጥ የአምላክን ህላዌ ሊያመላክትህ ቢችል እንጂ፣ እግዚአብሔርን በግል ለማወቅ ብቻውን በቂ አይደለም። ስለዚህ እግዚአብሔር ልዩ በኾነ መንገድ ራሱን ገለጠ። ይህም በታሪክ ውስጥ፣ በተወሰነ ቦታና ጊዜ ለአንድ ግለሰብም ይሁን ለአንድ ማኅበረ ሰብ የሰጠውን ልዩ መገለጥ ይመለከታል። ለምሳሌ ራሱን ለርእሳነ አበው ማለትም ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብና ለሌሎች ነቢያት እንዲሁም ለሕዝበ እስራኤል በልዩ ልዩ መንገድ የሰጠውን መገለጥ ዐይነት ማለቴ ነው። በመጨረሻም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ በሆነው በጌታችንና በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገለጡ የአስተርእዮው ሁሉ ዳርቻና ላዕላይ ከፍታ ነው። በዐጭሩ ቃሉ በኩል የተሰጠው መገለጡ ነው ልዩ የተባለው። አንድም አካላዊ ቃሉ፦ እሱም ክርስቶስ ነው፤ ሁለትም የተጻፈው ቃሉ፦ እሱም መጽሐፍ ቅዱስ ነው። አጠቃላዩ መገለጥ ፈጣሪ አምላክ መኖሩን ቢያሳይህም እንኳ ድኅነት አይሰጥህም፤ የሕያው እግዚአብሔርንም ማንነት፣ ባሕርይውንና ፈቃዱን በምልአት አታገኝበትም። 
  • ለእግዚአብሔር ስሙን ያወጣለት ማን ነው?


ቅዱሳት መጻሕፍት የእግዚአብሔር መገለጥ ማረጋገጫዎች እንደ መኾናቸው ስሙን ሰጥተውናል።

  • እነርሱም ላይ እንዴትእግዚአብሔርተብሎ ስሙ ሊጻፍ ቻለ ነዋ ጥያቄው። ስሙን ከየት አግኝተን ጻፍነው?


ስሙን የገለጠው እግዚአብሔር ራሱ ነው። ለምሳሌ ያህዌ የሚለውን የቃል ኪዳን ስሙን በደብረ-ኮሬብ ለሙሴ የነገረው ጌታ እግዚአብሔር ራሱ ነው።ሕዝቡን ሁሉ ከኀጢአታቸው ያድናቸዋልናጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ በሥጋዌው የተጠራበትን ስም ከእግዚአብሔር የተላከው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለቅድስት ድንግል ማርያም ነገራት። ሌሎች ስሞቹንም በተመሳሳይ መንገድ ማየት ይቻላል።

  • መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን ራሱን፣ ህልውናውን እና አሠራሩን ለመግለጽ በቂ መጽሐፍ ነው ማለት እንችላለን?

አዎን። እግዚአብሔር ማንነቱን፣ ሐሳቡንና ፈቃዱን ለመግለጥ ከመረጣቸው መንገዶች ዋነኛው በቅዱሳት መጻሕፍት የተነገረው ቃሉ ነው። ነገር ግን ቅዱሳት መጻሐፍት የሚነግሩን የተገለጠውንና በቂ የሆነውን ብቻ ነው። በቂ ነው ሲባል ግን ሊጻፍ ይቻል የነበረውን ሁሉ ይዟል ለማለት ሳይሆን፣ እንዲጻፍ የተገባውንና የመለኮት ፈቃድ የወሰነውን ሁሉ ይዟል ለማለት ነው። ይጻፍ ከተባለ ስለ አንድ በጠባብ ደረትና በዐጭር ቁመት ስለተወሰነ ግለ ሰብ እንኳ ብዙ ልትል ትችላለህ። ስለ ቴዎድሮስ፣ ስለ ሊንከን፣ ስለ ጋንዲ ወይም ስለ ማንዴላ ስንትና ስንት ቅጽ መጽሐፎች አላነበብንም እንዴ? ለማንኛውም እግዚአብሔርንና ፈቃዱን ለማወቅ ለእኔና ለአንተ አስፈላጊ የሆነው እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ የተነዳው ጸሐፊ ለተገለጠለት ነገረ መለኮታዊ አጀንዳ በቂ የሆነው ሁሉ ተጽፏልና መጽሐፍ ቅዱስ በቂ ነው። ርግጥ ያልተገለጠና ምሥጢር የሆነ መኖሩ እውነት ነው።
  • እግዚአብሔርን በተሟላ መልኩ መግለጽ ይቻላል? 

ከባድ ነው። ምክንያቱም እኛ እኮ ሰዎች ነን። በጊዜና ስፍራ ምጣኔ ክበብ የተወሰንን ነን። እግዚአብሔር ምጡቅና -ውሱን ነው። ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖራል። ማንንም ስለማይንቅና ራሱንም ለመግለጥ የሚወድ ከመሆኑ የተነሣ የሚገለጥ እንጂ የኀይሉ ብዛትና የታላቅነቱ ብርታት ከመታወቅ የሚያልፍ ነው። ብናውቅም የፈቀደልንን ያህል ብቻ ነው። የተገለጠልህን ያህል አንኳ ልግለጽ ብትልም የሰው ቋንቋና ጠገግ በቂ አይደለም። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስሦስተኛ ሰማይ በማለት እስከ ጠራው መንፈሳዊ ክበብ ተነጥቆ የተመለከተውን የነገረንሰውም ሊናገር የማይገባውን የማይነገረውን ቃል ሰማበማለት ነው።

  • እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የተመለሰ ጥያቄ ነው ማለት ይቻላል?

በሚገባ ማለት ይቻላል። እግዚአብሔር ላለመታወቅ ረቅቆና ርቆ የተደበቀ ሳይኾን፣ ለመታወቅ ቀርቦ የተገለጠ አምላክ ነው።አንድያ ልጁ ተረከውእስከ ተባለ ድረስ ለሰው ልጆች ጥያቄ የሚኾነው ምላሽ ተገኝቷል። ይሁን እንጂ መልሱን ሁሉም ተቀብሎታል ወይ የሚለው ሊያጠያይቀን ይችላል። ጌታ ኢየሱስ አምነው የሚድኑበትየማዕዘን ራስ ድንጋይየኾነውን ያህልየዕንቅፋት ድንጋይምነው።
  • ኢየሱስ የዕንቅፋት ድንጋይ?!

አዎን። ግን ለነማን ነው? አንዳንዶች ባለማመናቸው ይሰናከሉበታልና ነው። ካላመኑበት ወደ ተፈለገው ዓላማ ሳይደርሱ ወደቁ ማለት ነው። ለምሳሌ አንድ ሰውእንዴት አምላክ ሰው ይሆናል?ብሎ ሊሰናከል ይችላል። የእንቅፋት ድንጋይ ሆነበት ማለት ነው። ለማንኛውምሕይወት ተገለጠ አይተንማልያሰኘው የእግዚአብሔር መገለጥ ምልአት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመምጣቱ ብርሃን ታይቷል።
  • ይህም ሁሉ ኾኖ ግን ሰዎች በእግዚአብሔር ላይ ጥያቄ አላቸው። መልሱም የሚያሳርፍናበቃየሚያስብል አይደለም። ሁላችንም በተለያየ መጠን እስከ ህልውናው ድረስ እንጠይቃለን። ኹለት ሲደመር ኹለት አራት እንደ መሆኑ የሚያስማማ እምነት አይደለም በእግዚአብሔር ላይ ያለን። ቢመለስልን ለምን እንጠይቃለን?


ይኸውልህ፤ ብሌይዝ ፓስካል እንዳለውእግዚብሔር ራሱ ካልሞላው በቀር፣ ባዶ ወናውን የሚጮኽ መካነ ርቃን በየሰዉ ልብ አፉን ከፍቶ ይኖራል።ርሱን ስናገኘው ግን ማረፋችን እውነት ነው። ይህም ኾኖ ጥያቄዎች አሉን ወይ ብትለኝአዎንእላለሁ። እኔም ጥያቄ አለኝ። ጥያቄዬ ግን ህላዌውን አይመለከትም። በተለያየ ምክንያት ነው ጥያቄ የሚኖረን። አንዳንድ ጊዜ ጥያቄው ተመልሶም ባለማስተዋላችን የተነሣ በጥያቄነቱ የሚቀር ነገር ይኖራል። ሰዎች እኛው በምንፈልገው መልኩ የየራሳችንን ዓለም መቅረጽ እንፈልጋለን። የየራሳችን አማልክት የመኾን ኀጢአተኛ የውድቀት ዝንባሌ አለብን። እግዚአብሔር እኛ ሰዎች እንድንኾንለት የፈለገውን ወይም ዓለሙ እንዲኾንለት የሚሻውን ሳይኾን እኔ የምፈልጋትን የራሴን ዐይነት ዓለም መሥራት ያምረኛል። በዚያች ከንቱ ሕልሜ ውስጥ መሟላት ያለባቸው ሁሉ፣ ማንኛውም ነገር ወጪ ተደርጎና የሌሎች ሰዎች ፍላጎት ተደምስሶ፣ እንዲሟላልኝ እባትላለሁ። ጥያቄዎቻችን ያልተመለሱ የመሰለን እግዚአብሔር ስላልመለሳቸው ሳይኾን እኛ ስለማንኖረውና እንዲኾንም በማንፈልገው መንገድ ተመልሶ ሊኾን ይችላል። አንዳንዶች እኮ እንዳሻን የምንጠመዝዘው የየራሳችን አምላክ እንዲኖረን የምንዋትት ዐይነት ነን።
  • መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ነው ወይስ የቅዱሳን መንፈሳዊ የሕይወት ልምምድ ነው?

 የእግዚአብሔር ቃል ነው።  
  • እግዚአብሔር ብቻ?


አዎ፤ የእግዚአብሔር ቃል ነው። ይህ የሚሆነው በኹለት መንገድ ነው። አንደኛ በቀጥታ እግዚአብሔር የተናገራቸውን ቃሎች ስለ ያዘ ነው። ሁለተኛ የእግዚአብሔር ቃል የተገለጠው በሰው ልጆች ታሪክ፣ ባህል፣ ቋንቋ፣ ሥነ ጽሑፋዊና መንፈሳዊ ልምምድ ውስጥ ከመኾኑ ጋር ይያያዛል። ስለኾነም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሰው ንግግር ልታገኝ ትችላለህ። ከዚህ ተነሥተህአብርሃም የተናገረው የእግዚአብሔር ቃል ነው ወይ?” ብለህ ብትጠይቀኝአዎእልሃለሁ። የአብርሃምን ንግግር አብርሃም የተናገረውና የአብርሃም ቃል መኾኑን መጽሐፉ በማረጋገጥ ስለ ጻፈውና በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲካተት ስለተደረገ የእግዚአብሔር ቃል አካል ነው እንላለን ማለት ነው። “The Bible is the Word of God in all that it affirms.”  የምንለው ለዚህ ነው።
  • ከመንፈሳዊ የአገልግሎት ዘርፎች አንዱ መዝሙር ነው። በአሁኑ ጊዜ የወንጌላውያን መዝሙሮች በዘማሪያኑም ሆነ በመዝሙር ቅጂዎች መብዛት የተነሣ ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ይህን አንዳንዶች እንደ ወንጌላዊው ክርስትና መብዛትና መስፋፋት ሲያዩት ሌሎች ደግሞ እንደ ጥራት መዳከም አድርገው ይወስዱታል። እርስዎ የቱ ነዎት?

እንደ አተረጓጐሙ ነው። የእምነቱ መስፋት ምልክት አድርገው የሚወሰዱት ሊኖሩ ይችላል። ይህ ትክክለኛ አተያይ የሚኾንበትም መንገድ ይኖራል። እውነት የማይኾንበትም አጋጣሚ አይጠፋም። የእኔ እይታ በጕዳዩ ላይ የተሰጠ የማይም ድፍረት ሊኾን ይችላል። አንድም፣ የማወራው ጥናት ባላደረግሁበት ጕዳይ ላይ ነው። ሁለትም፣ ስለ ዝማሬ የማውቀው ወደምንም የቀረበ ትንሽ ነገር ነው።

ይኹንና ዝማሬ የእምነትህና የሕይወትህ ነጸብራቅ ነው። እምነቱን ወደ ገበያ ከወሰድነው ግን አንተ እንዳልከው የዝማሬ የጥራት መውረድ ሊመጣ ይችላል። ሰባኪያኑም ሆኑ ዘማሪያኑ አገልግሎታቸውን በሸቀጥ ደረጃ ካወረዱት አደጋው መከሠቱ አይቀርም።እግዚአብሔርን መምሰል ማትረፊያ በሚመስላቸው ሰዎችዘንድ በሚገኝ የነጋዴነት ግርግር ውስጥ የሚመጣ የጥራት መውረድ ሊኖር እንደሚችል ማሰብ አይከብድም ዘማሪዎቹም የትውልዳቸው ልጆች ናቸው እምነት ወደ ሸቀጥነት ደረጃ ከወረደ፣ ገበያ ሕግ የሚመራ ከሆነ፣ የሚሠለጥንበት የገበያ ቋንቋና መለኪያ ይሆናል ማለት ነው አገልግሎት ይቀርና ትርፍ ማጋበሻ ናል። ስለዚህ ዝማሬ ከሎሌነት ወደ ጌትነት የመስፈንጠር መሻት ክፉ ፈንታ አልገጠመውም ማለት አልችልም ከዚህ የተነሣ አንዳንዶች መዝሙር ተብለው ይቅረቡ እንጂ መዝሙር አይደሉም

  • በትክክለኛው ውድ ምንድን ነው መዝሙር ማለት? ወይም መዝሙር ምን መሆን አለበት?

ዝማሬ አምልኮተ እግዚአብሔር ላይ የሚያጠነጥን፣ እግዚአብሔርን የሚያከብር፣ የሚያልቅ፣ ውዳሴ አምላክ የተሞላ በቅዱሳ መጽፍት በተገለጸው እውነት መሠረት የእግዚአብሔርን ታላቅነት የሚያውጅ ማሕሌት ነው። የእኛን እሱን የመፈለግ፣ በእሱ ያገኘንውንም ድኅነትና እርካታ፣ የንስ መታደስን የሚያሳይ፣ ደካማነታችንን የሚገልጥና ወደ እሱ የሚያቀርብ ተማልሎም ነው። እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የገለጠው የድኅነት መንገድን ማወጅም ይጠበቅበታል። ስለዚህም መስቀሉ መካከለኛ ይሆንበታል። በጌታችን በኢየሱስ ቤዛዊ ሞት ያገኘነውን የኀጢአት ስርየትና በትንሣኤው የተቀዳጀነውን ድል ማብሠርም አለበት። እነዚህንና የመሳሰሉትን ያካትታሉየመጽ ቅዱሳዊ ዝማሬ ርያት

የዛሬዎቹ ግን በአንክሮ ሰብ የተጠመዱ ናቸው መልእክታቸውንም ብታይ የተዳከ ነውእኔ እንዲህ ነልኝ፣ እንዲህ ስለተደረገልኝ አድልዎ ተደርጎልኛል እንዲህ አደረግሁ ወዘተየሚ ፉከራ ይነቶች ናቸው። ይህም ሁሉ ኾኖ ግን በተገቢው መንገድ የሚሠሩ ጥቂት ትሩፋን አሉ እግዚአብሔርን ስለ እነርሱ ማመስገን ይኖርብናል የበላበንትን ወጪት እንዳንሰብርማለት ነው። አብዛኛውን ያየን እንደ ግን ገበያው የሚመራ ኾኗ የሚለው ነቀፋ ከእውነቱ ብዙ የራቀ አይመስለኝም

  • በዓለማዊ ዘፈኖች የክሊፖች ፋይዳ በራሳቸው ጥበብ ከመናችው ባሻገር የወጣውን አልበም ለማሻሻጥ ወይም ድምጻዊው/ ላይ መሆናቸውን እንዲመሰክር የሚ ነው። መንፈሳዊ መዝሙር ግን የሚፈጥርልን ሊናዊ ምስል በዓለም ከሚታየው በጣም የራቀ ነው። ይሁንና ዘማሪያኑ እንደዘፋኞች ሁሉ የግል ምቾትና ሳዊ ሀብታቸውን በሚያሳይ መልኩ ጭምር እየተ እንደ ዓለማዊው ዘፈኑን ከፍ በማድረግ ፋንታ የመዝሙሩን ዓላማ ዝቅ የሚያደርጉ ኾናሉ በግሌ መዝሙሮች ባይራላቸውና ያን ዓለም ሊናችን ብንመለከተው እመርጣለሁ። ለርስዎስ የክሊፖች ፋይዳ ምን መስሎ ይታይሃል?


ይህን የምመልስልህ በሙያዊ ውቀት ላይ ተመሥርቼ ሳይ (የለኝምና) እንደ አንድ ክርስቲያን የመዝሙር ክሊፖች ላይ ከሚሰማኝ ብቻ ተነ ነው። እናም ክሊፖች ከዝማሬ ጋር ተዛንቀው ለምን እንደሚ ግልጽ ከማይኾንላቸው ሰዎች እንደ አንዱ ነኝ

ምስላዊ እንቅስቃሴ ሲኖር መልእክቱን ለማስተላለፍ ይረዳ ይሆናል። ግን እሱስ ቢሆን ለዘማሪያኑ ተሳክቶላቸዋል ወይ ነው ጥያቄው። ብዙ የተሳካ አይመስለኝም። አንዳንድ ጊዜ መዝሙሩን ብቻውን ሰምቼ እወድደውና ክሊፕ መልኩ ሲመጣለካ ዘማሪው ለማለት ፈልጎ ነበር እንዴ?’’ ብዬ የደነገጥኩበት ጊዜ አለ። መዝሙሩን ሲዘምር እግዚአብሔርን ያመሰገንኩበት፣ ራሴንም ያየሁበት ዝማሬ ክሊ ተነጥፎለት ሲመጣ ከአንድ የበሰለ ክርስቲያን የማይጠበቅ ነብኝ ጊዜ አለ። መዝሙርነቱ ቀርቶፋሽን ሾውየሚመስልበት ጊዜ አለ። እርግጥ የቪዲዮግራፊ ባለሙያው ሙያው አኳያምስል ፈጥኖ ሲለዋውጥ ነው ይን የሚስበውብሎ ስለሚነግራቸው ዐሥር ጊዜ ልብስ መለዋወጥ ያስገርማል

አንዳንድ ጊዜ አስደንጋጭ ምስሎች ጭምር በክሊፖች ታሽገው ታያለህ። አልጋ ላይ ተኝተው ሊት ልብሳቸው ሲንከባለሉ ሶፋ ላይ ሲንፈላሰሱ፣ ቀለበት መንገድ ተደግፈው ታያለህ። መዝሙሩመንገዱን እንየሚል ቅስቀሳ ቢሆን ትርጕም ይሰጥሃል አሁን አሁን ሊናዬን ከጕድፍ ለማዳን ስለምፈልግ የመዝሙር ክሊፕ አላይም። ጥሩ ናቸው የምላቸውን መዝሙሮች በድም ብቻ ነው የምሰማቸው በምስል አላያቸውም።